ብዙኃን የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኃ/የተ/ህ/ሥ/ማህበር
የሥጋ ደዌ ተጠቂዎችና ሌሎች አካል ጉዳተኞች በሚደርስባቸው ከፍተኛ አድሎና የመገለል ጫና ምክንያት ከፍተኛ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች እንደሚደርስባቸው ይታወቃል፡፡ ከሚደርስባቸው ጫና በትግላቸው ለመላቀቅ የወሰኑ 51 ወንድ እና 24 ሴት በጠቅላላው 75 አካል ጉዳተኞች በመሰባሰብ ባዋጡት 11,000.00 /አስራ አንድ ሺህ/ ብር እና ከጀርመን ሥጋ ደዌ እና ቲቢ እርዳታ ማኅበር በተገኘ 25,000/ሃያ አምስት ሺህ/ብር የገንዘብ ድጋፍ በድምሩ 36,000.00/ ሰላሳ ስድስት ሺህ / ብር በመያዝ ሐምሌ 11 ቀን 2000 ዓ.ም በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ለሚገኙ የአካል ጉዳተኞች የብድርና ቁጠባ አገልግሎት የሚሰጥ ማሕበር መሠረቱ፡
ራዕይ
በአዲስ አበባ ከተማ ከሚገኙ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ህብረት ሥራ ማህበራት ውስጥ ግንባር ቀደም ተመራጭ እና እጅግ የተከበረ የቁጠባና ብድር ህብረት ሥራ ማኅበር ሆኖ ማየት፤
ተልዕኮ
አባላትን በተለያዩ የቁጠባ ዘርፎች በማሳተፍ ገንዘብ በማበደርና ካፒታል በማፍራት በወልም ሆነ በተናጠል የሀብት ባለቤት እንዲሆኑ ማድረግ፤
ግብ
በአባላት እጅ ተበታትነው የሚገኙትን ሀብቶች በቁጠባ በማሰባሰብ አዋጭ በሆነ የንግድ ወይም ሌላ ገቢ ማስገኛ ሥራ ውስጥ በማሳተፍ የተሻለ ገቢ እንዲያገኙ ማድረግ፤
ብዙኃን የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኃ/የተ/ህ/ሥ/ማህበር
የሥጋ ደዌ ተጠቂዎችና ሌሎች አካል ጉዳተኞች በሚደርስባቸው ከፍተኛ አድሎና የመገለል ጫና ምክንያት ከፍተኛ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች እንደሚደርስባቸው ይታወቃል፡፡ ከሚደርስባቸው ጫና በትግላቸው ለመላቀቅ የወሰኑ 51 ወንድ እና 24 ሴት በጠቅላላው 75 አካል ጉዳተኞች በመሰባሰብ ባዋጡት 11,000.00 /አስራ አንድ ሺህ/ ብር እና ከጀርመን ሥጋ ደዌ እና ቲቢ እርዳታ ማኅበር በተገኘ 25,000/ሃያ አምስት ሺህ/ብር የገንዘብ ድጋፍ በድምሩ 36,000.00/ ሰላሳ ስድስት ሺህ / ብር በመያዝ ሐምሌ 11 ቀን 2000 ዓ.ም በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ለሚገኙ የአካል ጉዳተኞች የብድርና ቁጠባ አገልግሎት የሚሰጥ ማሕበር መሠረቱ፡
የጀርመን ሥጋ ደዌ እና ቲቢ እርዳታ ማኅበር ለመነሻ ካፒታል በልግስና ከሰጠው የ25 ሺህ ብር የገንዘብ ድጋፍ በተጨማሪ ለቢሮ ግንባታና ለቁሳቁስ ማሟያ ተጨማሪ የ31,500 ብር ድጋፍ ማድረጉ ይታወቃል፡፡በወቅቱ ለተመሠረተው ማሕበር የተሰጠው ሥያሜ “የአዲስ አበባ ክልል ሥጋ ደዌ ተጠቂዎችና አካል ጉዳተኞች የገንዘብ ቁጠባና ብድር ሃላፊነቱ የተወሰነ የህብረት ሥራ ማህበር” የሚል ነበር፡፡
የአባልነት ቅጽ
Our team of experienced professionals combines technical expertise, industry knowledge, and a deep understanding of our clients’ needs to deliver exceptional results.
ቁጠባ
01.
መደበኛ ቁጠባ
ማንኛውም የኅብረት ሥራ ማኅበሩ አባል የሆነ የማህበሩን መነሻ ወይም ዝቅተኛ መደበኛ ቁጠባ ብር 500 ሳያቋርጥ በየወሩ መቆጠብ ይኖርበታል፡፡ አንድ አባል የቆጠበውን መደበኛ ቁጠባ ማውጣት የሚችለው ከአባልነት ሲለቅ ብቻ ነው፡፡
አንድ አባል የንግድ ሥራ ለመጀመርም ሆነ ለማሻሻል ቢፈልግ ለስድስት ወር በተከታታይ ሳያቆርጥ የሚወስደውን ብድር መጠን 25% (በመቶ) የቆጠበ እና 5% እጣ የገዛ አባል የንግድ ሥራ መጀመሪያ ወይም ማሻሻያ ብድር ለመጠየቅ ብቁ ይሆናል፡፡
02.
የፍቃደኝነት ቁጠባ
አንድ አባል ከመደበኛ ቁጠባ በተጨማሪ የፍላጎት ቁጠባ መቆጠብ ይችላል፡፡ ይህንንም ቁጠባ በማንኛውም ጊዜ ወጪ ማድረግ ይችላል፡፡
03.
የግዜ ገደብ ቁጠባ
አንድ አባል በግዜ ገደብ ሲቆጥብ ለቆጠበው ቁጠባ በዓመት 10 በመቶ የተቀማጭ ወለድ ይታሰብለታል፡፡
04.
ለቤት ግዥ ቁጠባ
አንድ አባል ለተከታታይ ስድስት ወራት ከብድር ጥያቄው 35% የቆጠበ እና 5% እጣ የገዛ አባል የቤት ግዥ ብድር ለመጠየቅ ብቁ ይሆናል፡፡
05.
ለመኪና ግዥቁጠባ
አንድ አባል ለተከታታይ ስድስት ወራት ከብድር ጥያቄው 30% የቆጠበ እና 5% እጣ የገዛ አባል የመኪና ግዥ ብድር ለመጠየቅ ብቁ ይሆናል፡፡
06.
የሴቶችና ወጣቶች ቁጠባ
የሴቶችና ወጣቶች ቁጠባ ወደፊት የተሻለ ህይወት እንዲመሩ አዋጪ በሆነ የገቢ ማስገኛ ስራዎች ላይ እንዲሰማሩ ከስልጠናና የማማከር አገልግሎት ጋር ብድር ይመቻቻል፡፡
07.
የወል ቁጠባ /የትምህርት፣የክብረ በዓላት፣የህክምና/
አንድ አባል ከመደበኛ ቁጠባ በተጨማሪ የትምህርት፣የክብረ በዓላት፣የህክምና/ ቁጠባ መቆጠብ ይችላል፡፡ ይህንንም የወል ቁጠባ በታቀደለት ጊዜ ወጪ ማድረግ መጠቀም ይችላል፡፡
08.
የልጆች ቁጠባ
የማኅበረሰቡ የመቆጠብ ልምድ እንዲያድግ ማንኛውም ሰው በኅብረት ሥራ ማህበር ውስጥ እንዲገባና እና ልጆቹንም አባል እንዲያደርግ ያመቻቻል፡፡በተጨማሪም ወላጆቻቸውን ላጡ ህፃናት ከወለድ ነፃ ብድር ያመቻቻል፡፡
09.
የቁጠባ ወለድ
አንድ አባል ለቆጠበው መደበኛ ቁጠባ በዓመት 7% (በመቶ) የተቀማጭ ወለድ ይታሰብለታል፡፡
የማሕበሩ የሥራ አመራር ቦርድ አባላት
አቶ ኣዳነ ዋለ
/ሰብሳቢ/
Red Kidney Beans
አቶ ይርጋለም ኃይሌ
ም/ሰብሳቢ/
አቶ በውቀቱ አስማማው
/ፀሐፊ/
ወ/ሪት ሀብታም ጆቴ
/ሂሳብ ሹም/
መ/ርት ይታይሽ እስተመች
/አባል /
ወ/ሪት አባይነሽ ታከለ
/ገንዘብ ያዥ/
